Sunday, 2024-04-28, 8:34 AM
ETHIOPIAN POLITICS current event and news
Main Registration Login
Welcome, Guest · RSS
Site menu
    news
    news
    curency
    Calendar
    «  October 2011  »
    SuMoTuWeThFrSa
          1
    2345678
    9101112131415
    16171819202122
    23242526272829
    3031
    Site friends
     
    Main » 2011 » October » 10 » የኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ በኦስሎ፣ኖርዌይ
    10:39 PM
    የኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሰልፍ በኦስሎ፣ኖርዌይ

    የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በዛሬው ዕለት በኖርዌይ መዲና ኦስሎ በሚካሄደው የኃይል አቅርቦት ተመልካች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አሁን እዚያው ይገኛሉ።

     

    የኖርዌይ መንግሥት እና ዓለም አቀፉ የኃይል አቅርቦት ጉዳይ ተመልካች ድርጅት በጋራ ያዘጋጁት ይኸው የሁለት ቀናት ጉባዔ የኃይል አቅርቦትን በተለይ በአዳጊዎቹ ሀገሮች ላሉት ለድሆች ማዳረስ የሚቻልበት ዘዴ እንዴት ሊሻሻል ይችላል ለሚለው ሀሳብ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየተወያየ ነው።የጉባዔው አዘጋጂዎች ብራዚል፡ ኢትዮጵያ፡ ሕንድ፡ ላይቤሪያ እና ደቡብ አፍሪቃ ይህንኑ ሀሳብ ተግባራዊ ለማድረግ በጀመሩት ጥረታቸው ላይ አብረው በአጋርነት እንዲሰሩም ጋብዘዋቸዋል። ጉባዔው በሚካሄድባት በኖርዌይ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በኦስሎ ከተማ ጉባዔው በሚደረግበት አዳራሽ ደጃፍ በመሰብሰብ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ አንጻር ተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል። የተቃውሞ ሰልፉን ያዘጋጀውን የኢትዮጵያውያኑን የግብረ ኃይል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዶክተር ሠይፉ ፀጋዬን አርያም ተክሌ በስልክ አነጋግራዋለች፤ በመጀመሪያም የተቃውሞ ሰልፉ ዓላማን እንዲያብራሩላት ጠይቃቸዋለች።

    አርያም ተክሌ

    ሸዋዬ ለገሠ

    Views: 597 | Added by: dani | Rating: 4.0/1
    Total comments: 0
    Name *:
    Email *:
    Code *:
    Copyright MyCorp © 2024
    Create a free website with uCoz