"በሽብር” ተግባር ተጠርጥረው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከሚገኙት እስረኞች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ /ኢብአፓ/ ፕሬዝደንት አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር፣ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ጋዜጠኛ ርዕዮትዓለሙና ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በትላንትናው ዕለት ፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ ተቀጥሮ የነበረው በክስ አቀራረቡ ላይ የተከሳሽ ጠበቆች ባቀረቡት ተቃውሞ ክሱ እንዲሻሻል ፍ/ቤቱ ብይን በመስጠቱ ነው፡፡ ተሻሽሎ በቀረበውም ክስ በተመሳሳይ ሁኔታ ጠበቆች ቅሬታ በማቅረባቸው ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሚ ለብይን ለዛሬ ተቀጥሯል፡፡
...
Read more »