በሽብር ተግባር ተሰማርታችኋል በሚል የፈጠራ ክስ የተከሰሱ፣ በአገር ቤት ሰላማዊ በሆነ መንገድ የኢትዮጵያ ሕዝብ መብቱና ነጻነቱ እንዲረጋገጥለት በመታገል የሚታወቁት የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አራጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ አቶ እስክንድር ነጋ ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዉያን የቀረበባቸዉን ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ የወሰነ ሲሆን ፣ የቀረበባቸዉ ክስ መሰረት የሌለዉ እንደሆነ በመግለጽ ጥፋተኛ እንዳልሆኑ አረጋግጠዋል። በተለይም አቶ አንዳዋለም አርጌ «ጥፋተኛ ነህ ? » ለሚለዉ የፍርድ ቤት ጥያቄ "ይኼ ክስ በኢትዮጵያ የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል ለማፈን የተዘጋጀ የውሸት ዲሪቶ ነው” በማለት ያጣጣለዉ ሲሆን ምንም አይነት አስተያየት ለመስጠት ፍቅደኛ እንዳልሆነም ሪፖተር ዛሬ ባወጣዉ እትሙ ዘግቧል።
...
Read more »